የስፖርት ዜናዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ከአንጎላ አቻው ጋር ትናንት ሉዋንዳ ውስጥ ተጋጥሞ 1 ለባዶ ተሸንፏል። ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል ለዓለም የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ሚያሚ ውስጥ ለዋንጫ ይገናኛሉ። በሜዳ ቴኒስ ጥቁር አሜሪካዊቷ ሴሬና ዊሊያምስን በድል ጎዳና የሚያቆማት አልተገኘም። ጀርመናዊቷ ተፎካካሪዋን ከኋላ ተነስታ ድል ነስታለች።