ሀገር የኮምፒዩተር ቫይረስና ሀከር ነው እንዴ?
![]() |
ከዓመታት በፊት የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት አባሎችና ሌሎች ሰዎች ተከሰው ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ”የቅንጅት አመራሮች የፍርድ ቤት ውሎ” በሚል ርእስ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ተከታታይ ዘገባ አቀርብ ስለነበር ችሎቱ እስኪጠናቀቅ አንድም ቀን ከፍርድ ቤት ቀርቼ አላውቅም ነበር። በዚህም የተነሳ ክሱና የክርክር ሂደቱ ምን እንደሚመስል መናገር የሚያስችል መረጃ አለኝ ለማለት እደፍራለሁ።
