የኢራቅ አማፅያን ግስጋሴ

የኢራቅ ኩርዶች የሰሜናዊቷን የነዳጅ ዘይት አምራች ከተማ የኪርኩክን አንዳንድ አካባቢዎች በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል የዓይን ምስክሮችን ጠቅሶ ዘግቧል ። ትናንት ሞሱልንና ቲክሪትን የተቆጣጠሩት የኢራቅ ሱኒ አማፅያን ደግሞ ይዞታቸውን በማጠናከር ወደ ኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድ ለመገስገስ መዛታቸው ተሰምቷል ።