በዩጋንዳ-ካምፓላ ሁለት ፈንጂዎች ፈንድተው ከ64 በላይ ሰዎች ሞቱ

አንዱ ፈንጂ በኢትዮጵያዊያን ሬስቶራንት ውስጥ ፈንድቷል

Ethiopia Zare (እሁድ ሐምሌ 4 ቀን 2002 ዓ.ም. July 11, 2010)፦ በዩጋናዳዋ መናገሻ ካምፓላ ራግቢ ክለብ በተባለ ቦታና የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ውድድርን ለመከታተል በአንድ የኢትዮጵያ ሬስቶራንት ውስጥ በተሰባሰቡ ሰዎች መሀል በፈነዱ ሁለት ፈንጂዎች ምክንያት በርካታ ኢትዮጵያኖችን ጨምሮ 64 ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ።