የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አዲስ የፍጥነት መንገድ

ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ የሚወስድ አንድ አዲስ የፍጥነት መንገድ ትናንት ተመርቆ ተከፈተ። ከሁለት ሳምንታት በኋላ በይፋ ለተሽከርካሪዎች የሚከፈተውን መንገድ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋ ባንድነት መርቀው የከፈቱት ኢትዮጵያን የጎበኙት የቻይና ጠቅላይ ሚንስትር ሊ ኬኪያንግ ናቸው።