የኢራቁ ምክርቤታዊ ምርጫና ፍጥጫ

የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ከኢራቅ ጠቅልሎ ከወጣ በኋላ የመጀመሪያውን ምክር ቤታዊ ምርጫ ኢራቃውያን ረቡዕ፤ ሚያዝያ 22 ቀን፣ 2006 ዓም አከናውነዋል። በከፍተኛ ጥበቃ ነው የኢራቅ ምርጫ የተከናወነው። በኢራቁ ምርጫ ለመምረጥ ከተመዘገበው ነዋሪ ሲሦው ድምፁን መስጠቱም ተገልጿል።