ምርጫ ዲሞክራሲ በራቃት አልጀሪያ

አልጀሪያን እጎአ ከ1998 አንስቶ ለ16 ዓመታት በሦስት የፕሬዚዳንትነት ዘመናቸው አንቀጥቅጠው ገዝተዋል፤ ፕሬዚዳንት አብደልአዚዝ ቡተፍሊካ። ካለፈው ዓመት አስንስቶ በነርቭ ዕክል በሽታ የሚሰቃዩት የ77 ዓመቱ አዛውንት ስልጣን ዛሬም አልበቃኝም፥ ለአራተኛ ጊዜ መጥቻለሁ ብለዋል። የፊታችን ሐሙስ ለፕሬዚዳንትነት ለመወዳደር ዕጩ ሆነው ቀርበዋል።