የግንቦት ሰባት/ኢሳት እና የብርሃኑ ዳምጤ የፖለቲካ ዝሙት ሲዳሰስ… ክፍል አንድ

ከዚህ ቀደም የብርሃኑ አባነጋን መንሸራተት አስመልክቶ የፖለቲካ ሽርሙጥና እንደሆነና ግለሰቡም የፖለቲካ ዝሙት በመፈጸም ላይ እንደሆነ ቢገለጽም ሰሚ ጆሮ ለማግኘት አልታደልንም :: አዎ እንደ ግንቦት ሰባት እና እንደኢሳት ያሉ የዲያስፖራው መስታዎቶች ሊያዳምጡን ፍቃደኛ ካለመሆናቸውም በላይ እነሱ የሚያዳምጡት የወያኔን ዝሙተኛ ፖለቲከኞችን ስለሆነ መለማመጥን አንፈልግም:; ደስ ካላቸው ደስ ይበላቸው ደስ ካላላቸው ገደል ይግቡ ….. እኛ ግን ኢትዮጵያዊነታችንን የሚነጥቀን በነጻነት የምንተነፍሰውን ሃሳብ የሚገድብ ምንም ነገር አይመጣም…. እኛም አናቆምም …
በመጀመርያ ደረጃ ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር በሻእቢያ እና በወያኔ መካከል ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ልውውጥ በፓርቲ ደረጃ እንደሚካሔድ እና ሁለቱ ጸረ ኢትዮጵያ አቋማቸው ያንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ መሆኑ ልንቀበለው የሚገባ ጉዳይ ነው:: አለም ሰልጥኖ ወደ አንድነት በማምራት በሰው ልጆች መካከል ያለ የቀለም እና የዘር ልዩነትን ለማጥፋት እና በቴክኖሎጂ እውቀት ተመንጥቆ ለመሄድ በሚሰራበት ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ባረጀ እና ባፈጀ የጎሳ ፖለቲካ ጥያቄ ህዝብም ውስብስብ መንገድ ላይ በመጠላለፍ ለመከፋፈል እና ጠንካራ ሃገራዊነትን ለማዳከም የሚሰሩ ስራዎችን ልብ ብለን ማጤን እንዳለብን ለማስታወስ እገደዳለሁ:;
ብርሃኑ ዳምጤ አሊያም አባመላ በመባል የሚታወቀው የፖለቲካ ግልሙተኛ እና ሴሰኛ ግለሰብ ማረፊያ ያጣበትን ተሌኮ ለማስፈጸም በሚያደርገው መራወጥ ውስጥ ራሱን ግንቦት ሰባት ብሎ ከሚጠራው ድርጅት ጋር የፖለቲካ ዝሙት ሲፈጽም ቆይቶ በሁለት ስለት ቢላዋ በማረድ የራሱን እና የሌሎችን ደም በአደባባይ ለማፍሰስ ቆርጦ የተነሳ እና ያልተሳካለት ግለሰብ ነው::
ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር ይህ ግለሰብ ትክክል ነው ይህ ግለሰብ ትክክል አይደለም የሚለው ነገር እንደተጠበቀ ሆኖ የደፈረሰው መጥራት እንዳለበት በግልጽ ለመናገር እፈልጋለሁ::
ብርሃኑ ዳምጤ አባመላ በሚለው የፓልቶክ ፕሮግራሙ አጀማመሩ የወያኔን በልማታዊነት ሽፋን የሚሴረውን የጎሳ ፖለቲካ እና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በዲያስፖራው ውስጥ ለማስረጽ የፕሮፓጋንዳ ስራ ሲሰራ ቢቆይም ሊሳካለት አለመቻሉ ጸረ ወያኔ አቋም እንደያዘ ተደርጎ በሰርጎ ገብነት ከወያኔ በወረደለት ትእዛዝ አባካኝነት እና ከሻእቢያ ጋር በተደረገ የመረጃ ልውውጥ በሻእቢያ የነገር አባትነት ከግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር የፖለቲካ ዝሙት እንዲፈጽም ተደረገ:: የፖለቲካ ዝሙቱ በእርካታ ታጅቦ በኢሳት የሳምንቱ እንግዳ ሆኖ ወያኔ በማሳጣት እና በመዝለፍ በሰርጎ ገብ የቆረጣ ታክቲክ የኢሳት ጋዜጠኞችን በማወዳደስ ግንቦት ሰባትን በማንቆለጳጰስ ራሱን ከተቃዋሚዎች ጎራ አሰልፎ የነበር ሲሆን እንዲሆን አክራሪዎች አሸባሪዎች ሲላቸው የነበረውን የኢትዮጵያውያንን ሙስሊሞች ትግል ለመጠጋት በመሞከር ቢያሞጋግስም አናቱን በፍልጥ ስላልነው ሳይሳካለት ቀርቶ አፉን ይዞ ተቀመጠ:: ዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሲኖር ከነበረው ከጃዋር መሃመድ ጋር ማታ ማታ ሻይ ቡና እያለው የኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎችን ፖለቲካ በማጥላላት እና በወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ሲያጠምቀው የነበረው አባመላ ዞር ብሎ አዛኝ በመምሰል በጃዋር መሃመድ ላይም ጸር የሆኑ ቃላቶችን ሲተፋ እንደነበር ሲታወቅ አባመላ ራሱ ጃዋርን በጥላቻ ሲያሰለጥነው እንደነበር የማይዘነጋ እውነት ነው::
ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ብሎ ራሱን የሚጠራው ድርጅት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንን እንደማይወድ እና ከጀርባው በሻእቢያ እየተጠመዘዘ የጸረ ኢትዮጵያ አቋም ማራመጃ መሆኑ የማይካድ ሃቅ ነው:: እንደ ኢሳት ባሉ በዲያፖራው ሃብት በሚተዳደሩ ሚዲያዎች የፖለቲካ ትግል እና የለውጥ አማራጭ ሃሳብ ያላቸው ኢትዮጵያውይና እንዳይቀርቡ እና እንዳይጠቀሙ በማገድ የወያኔ ትርፍራፊ የፖለቲካ ጋለሞታዎች እንዲዘፍኑበት መደረጉ አሌ የማይባልበት ጉዳይ ሲሆን በዚህ ጉዳይ ላይን ራሱ የሚዲያ ነጻነቶችን በመጋፋት ለውጥ ከማምጣት ይልቅ ነጻነቶች በሻእቢያና ወያኔ ተላላኪዎች በተዘዋዋሪ ሲቀበሩ እያየን ነው::
እንደ ግንቦት ሰባት ያሉ ድርጅቶች በፖለቲካ አማራጭ ሃሳብ የያዙ እና ለውጥ በማምጣት ረገድ ሚና መጫወት የሚችሉ ኢትዮጵያውያንን በመግፋት የወያኔ ሰርጎ ገብ ወንበዴዎችን በአመራር እና በድርጅታቸው የደህንነት መዋቅር ውስጥ በማስገባት ራሳቸውን ከትግሉ ውጪ ለመጠለዝ እየተወራጩ ይገኛሉ:; ኢሳት የሚዲያ ተቋም ተብሎ እስከተቋቋመ ድረስ ማድረግ የሚገባውን የማያውቅ እና ባልበሰሩ ሰዎች እና የጋዜጠኝነት ልምድ ባሌላቸው እንዲሁም በሳል እና ሚዛናዊ መረጃዎችን ባልያዙ ደረቅ ተንታኞች ታጅቦ የሞት ጉዞውን እያፋጠነ ነው::
ወያኔ በብርሃኑ ዳምጤ በኩል በአባቱ ሻእቢያ አዝማችነት የመጀመሪያ ዙር ስራውን አጠናቆ ብርሃኑ ዳምጤን ወደ ልማታዊ ጋዜጠኝነት መልሶታል:; በሃገር ወዳድነት ሽፋን በማስመሰል የተካነው ብርሃኑ ዳምጤ ድራማውን አጠናቆ ዲያስፖራ ተቃዋሚዎችን በመዝለፍ ስራ ላይ ተመልሶ ተሰማርቷል:: ካሁን በኋላ የአባመላ ፓልቶክ እንግዶች እንደ ጃዋር እና ዘርኣይ ያሉ የጥላቻ ፖለቲካ ስልጥኡኖች ናቸው:;ከሃገር ቤት የተሰራውን የወያኔን ድራማ እና የሚሚ ስብሃቱን ጸረ ግንቦት ሰባት እና ኢሳት ውንጀላ እና ትችት ተከትሎ የብርሃኑ ዳምጤ ትፋት ምን እየተሰራ እናዳለ እና የዲያስፖራውን የለውጥ ፖለቲካ ገደል ለመክተት በህዝብ የመኖር ህልውና ላይ ፍርሃት እና ሽብር ነዝቶ ወያኔን በስልጣን ለማቆየት የተሸረበውን ሴራ በገሃድ ያሳያል::
ከዳዊት ከበደ እና ከጃዋር የሰርጎ ገብ ፖለቲካ ያልተማሩት ግንቦት ሰባት እና ኢሳት ሃገር ወዳድ እና ብዙ ስራዎችን ሊሰሩ የሚችሉ ኢትዮጵያውያንን ወደ ጎን በማግለል በዙሪያቸው እንደብርሃኑ ዳምጤ ያሉትን ሰርጎ ገቦች በመኮልኮል ያላዋቂ ሳሚ … ሆነው ህዝቡን … በመለቅለቅ ላይ ይገኛሉ::ኢሳት አንድ ሃገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ በፕሮግራሞቹ ላይ ከማቅረብ ይልቅ የወያኔ ኮልኮሌ የመረጃ ሰዎች እና ሰርጎ ገቦችን ቢያቀርብ ያተረፈ እየመሰለው በፖለቲካ ኪሳራ ውስጥ ገብቶ ከሕዝብ ልሳንነት ይልቅ የግንቦት ሰባት ልሳን እንደሆነ እያንጸባረቀ ነው:: ኢህኣፓ በተፋቻቸው እንደ ብርሃኑ ነጋ ባሉ የፖለቲካ ሰልባጆች ትእዛዝ የሚመራ አስመስሎበታል:: እንደ ነእመን ዘለቀ ባሉ በሻእቢያ እና ወያኔ ትራፊዎች የሚመራው ኢሳት አጀማመሩ መልካም ቢመስልም ግን በጀት አይለቀቅልህም ከወያኔ ከዳሁ የሚሉ ግለሰቦችን እያባዛህ ካላቀረብክ የተባለ ይመስል ነጋ ጠባ የምናያቸው የወያኔ ሰዎችን መሆኑ አሳሳቢ አድርጎታል::ስለዚህ ግንቦት ሰባት እና ኢሳት ከወያኔ ሰርጎ ገቦች ጋር የፖለቲካ ዝሙት እየፈጸሙ የህዝብን ትግል እየገደሉት ነው ቢባል ድፍረት አይሆንም:: ለዛሬ በዚህ ይብቃ ጹሁፉ ቀጣይ ነው ይጠብቁት::