የዩክሬይን ጊዜያዊ ሁኔታ

የዩክሬይን ሁኔታ ገና አልሰከነም፤ በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቃዊ ከፊል በክሩሚያ ልሣነ-ምድር ፤ በሩሲያ ተጻራሪና ደጋፊ ዩክሬናውያን ዘንድ ግጭት እንደነበረ ተነግሯል። በኪቭ፤ ከሥልጣን የተወገዱትን ፕሬዚዳንት ቪክቶር ያኑኮቪችን የተካው አዲስ አስተዳደር፤ በእርሳቸው የአስተዳደር ወቅት የነበሩ የተቋሞችን መርኆዎች በመሻር ላይ ነው።