አቡጊዳ – ከ50 ሺሆች በላይ የሚሆን ሕዝብ ጨዋነቱን እና ሰላማዊነቱን በባህር ዳረ አረጋገጠ ( የሰልፉን አስደናቂ ቪዲዮ ይመልከቱ)
በባህር ዳር የተደረገው ሰላማዊ ስለፍ፣ በጣም አስደናቂና አስደሳች እንደነበረ የተለቀቁ ኦዲዮዎች፣ ቪዲዮዎች ይናገራሉ። ሰልፉ እንደተጀመረ ከ15 ሺህ በላይ እንደነበረ በሚሊዮነም ድምጽ ለነጻነት ፌስ ቡክ ገጽ የተገለጸ ቢሆንም፣ ሰልፉ በቀጠለ ቁጥር ፣ ሕዝቡ ከየአካባቢዉ ሰልፉን እየተቀላቀለ፣ ቢያንስ ከአምሳ ሺሆች በላይ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል።
በፎቶዎች እና ቪዲዮዎች እንደሚታየው፣ ሰልፈኞቹ ኮከብ የሌለበትን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ እያዉለበለቡ፣ መፈክሮችን እያሰሙ፣ በደስታ ለነጻነት፣ ለመብት መከበር፣ ለሕግ የበላይነት ለአንዲት ኢትዮጵያ አንድነት ይጩሁ ነበር።
ምንም እንኳን የብአዴን የደህንነት ሰራተኞች በአለቆቻቸው ታዘዉ ረብሻና ሁከት ለመፍጠር ሙከራ ቢያደርጉም፣ አንድ ሰው ላይ ጉዳት ሳይደርስ፣ አንዲት ጠጠር ሳትወረወር፣ ሰልፉ በሰላም ተጀመሮ በሰላም ተጠናቋል። የባህር ዳር ህዝብም ጨዋነቱን፣ አስተማሪነቱን፣ ሰላም ወዳድነቱን እና አንዳንድ የሰለጠን ሕዝብ መሆኑ አረጋግጧል።
