ሙጋቤ፡ አምባገነን መሪ ወይስ የነፃነት አርበኛ

የዚምባብዌ ፕሬዚደንት ሮበርት ሙጋቤ ትናንት ዘጠናኛ ዓመታቸውን አከበሩ። ምዕራቡ ዓለም ጨካኝ አምባገነን አድርጎ የሚመለከታቸው ሮበርት ሙጋቤ በአፍሪቃ ብዙ ደጋፊዎች አሉዋቸው። ይሁንና፡ ሙጋቤ አምባገነን ናቸወ የሚለውን አነጋገር በለንደን የሚታተመው ሳምንታዊ መጽሔት «ኒው አፍሪካ» ዋና አዘጋጅ ባፉር አንኮማ መሠረተ ቢስ ሲል አጣጥሎታል።