የእኛ ታሪክና የፖለቲካ ውጥንቅጥ
ጥቂት አሳቦች በሞገደኛው ተክሌ ወሥርጉተ ሥላሴ ጽሑፎች ላይ (ክፍል-፩-)
ዲ/ን ኒቆዲሞስ ዕርቅ ይሁን
ሥርጉተ ሥላሴ የተባሉ ጸሐፊ በተለያዩ ጊዜያት የሚጽፏቸውን በአብዛኛው ታሪካዊ የሆኑ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርስ አዘል፣ በኃይለኛው አገራዊ/ኢትዮጵያዊ ዘዬ፣ ትውፊትና ባህል የተጫነው የሚመስለውንና፤ እንዲሁም ምክርና ትችት ዘመም የኾኑ፣ እንዲያም ሲል “የኢትዮጵያዊነት ወኔና ስሜት” በእጅጉ ጎልቶ የወጣበትንና ያየለበትን መጣጥፎቻቸውን ለማንበብ ዕድሉ ገጥሞኛል።