ስደተኞችና አደገኛው የባሕር ላይ ጉዞ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች መርጃ ድርጅት በምህፃሩ IOM ባወጣው ዘገባ ባሳለፍነው የጎርጎሪዮሳዊው 2013 ዓመት በርካታ የሶሪያ፣ የኤርትራና የሶማሊያ ስደተኞች በአደገኛ የባሕር ላይ ጉዞ አውሮጳ መድረሳቸውን አትቷል።