የኢትዮጵያ የባቡር ሀዲድ ፕሮጅክቶች

ኣገራዊም ሆነ ኣህጉራዊ ልማት ሲታለም ኣስቀድሞ መታሰብ ያለበት ነገር ቢኖር የመሰረተ ልማት ኣውታሮች ዝርጋታ መሆኑ ኣያጠያይቅም። ኣንዱና ዋናው ደግሞ መንገድ ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም። በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሰፋፊ እና ከባህር በር ፈንጠር ብለው ለሚገኙ ኣገሮች የባቡር ሀዲድ ኣስፈላጊ ብቻም ሳይሆን ወሳኝነትም ኣለው ተብሎ ይታመናል።