የደቡብ ሱዳን ስምምነትና ገቢራዊነቱ

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች፤ በፕሬዚደንት ሳልቫኪር የሚመራው የጁባው መንግስት እና የቀድሞው የኣገሪቱ ምክትል ፕሬዚደንት ሪክ ማቻር የሚመሩት ኣማጺ ቡድን ተወካዮች ትናንት ማታ የተኩስ ኣቁም ስምምነት ተፈራርመዋል። አዲስ አበባ ዉስጥ የተፈረመዉ ሥምምነት ገቢራዊ የሚሆንበት መንገድ ግን እንዳጠያየቀ ነዉ።