ክህደት ከአናት ሲጀምር
በቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ
እውነት ቤት ስትሠራ … ውሸት ላግዝ ካለች
ሚስማር ካቀበለች … ጭቃ ካራገጠች
ቤቱም አልተሠራ … እውነትም አልኖረች።
… እንደዚያ ነው በባቢሎን ዘመን። የአንዱ ቋንቋ ከአንደኛው ይዘበራረቃል … መግባባትና መረዳዳት ብርቅ ይሆናል። በጠራ አማርኛ የተጣፈውን በጉግማንጉግኛ በመተርጐም ከውስጡ የሚፈልጉትን ብቻ አለፍ አለፍ እያሉ ያነቡታል። እናም የራሳቸውን ትርጉም ይሰጡታል። ፍየል ወድያ … ቅዝምዝምም ወዲህ ይሆናል።