IOM ለተመላሾች ተጨማሪ እርዳታ መጠየቁ

በፍልሰት ሳቢያ በሚከሠቱ ችግሮች ላይ በማትኮር የተለያዩ አጣዳፊ የርዳታ ዓይነቶችን የሚያቀርበው ዓለም አቀፍ ድርጅት (IOM) ከስዑዲ ዐረቢያ ተገደው የተመለሱ ኢትዮጵያውያንን በመርዳት ላይ ሲሆን የተረጂዎቹ ቁጥር ከፍ በማለቱ ተጨማሪ እርዳታ እንዲቀርብለት መማጸኑ ተመልክቷል።