አምሥተኛ ዓመት የሆነው የ«አታላንታ» ተልዕኮ

የአውሮጳ ህብረት ለመጀመሪያ ጊዜ የጦር ተልዕኮ ለማካሄድ የወሰነው በአፍሪቃ ቀንድ የሚታየውን የባህር ላይ ውንብድናን ለመታገል ቆርጦ በተነሳበት ጊዜ ነበር። « አታላንታ» በሚል መጠሪያ የሚታወቀው እና ከአምሥት ዓመት በፊት የተጀመረው ይኸው የኅብረቱ ፀረ የባህር ላይ ወንበዴዎች ተልዕኮ የተሳካ ውጤት ማስገኘቱ ነው የሚነገረው።