ዉይይት ሥለ ኢትዮጵያ ስደተኞች

በመካከለኛዉ ምሥራቅ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ሥደተኞችን ችግር ለመግታት የተቀናጀና መጠነ-ሠፊ ጥረት መደረግ እንዳለበት ዋሽግን-ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በጉዳዩ ላይ የተነጋገሩ ተሰብሳቢዎች አስታወቁ። ባለፈዉ ቅዳሜ በተደረገዉ ዉይይት ላይ የተካፈሉ ምሑራን፥ የሕግ ባለሙያዎችና የማሕበራት መሪዎች ጥናታዊ ፅሑፍ አቅርበዉ ነበር።