የዕዉቀት ልውውጥ፣ አፍሪቃዉያን ጠበብት በጀርመን

«እዉቀት ለነገ» በሚል መርህ ከስድሳ የሚበልጡ ከሰሃራ በታች የሚገኙ አፍሪቃዉያት ሀገራት ምሁራንን ጭምር ያሳተፈ የሁለት ቀን ጉባዔ ጀርመን ሃኖቨር ከተማ በሚገኘዉ የፎልክስቫገን ተቋም ተካሂዶአል። ጉባዔው በአፍሪቃ በማህበራዊ፤ በሳይንስ፤ በህክምና፤ እንዲሁም በሃይማኖት ረገዶች በሚደረገዉ ሳይንሳዊ ምርምር ሥራ ላይ ተወያይቶአል፤