ትራምፕ ለአሜሪካ ከፈጣሪ የተላኩ መሪ ናቸው ብለው የሚያምኑት ቀኝ ዘመም ክርስቲያኖች
በአሜሪካ ምርጫ የፖለቲካ እና የምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ብቻ አይደሉም ዋነኛዎቹ መጠንጠኛዎቹ። የክርስትና ሃይማኖትም በአገሪቱ መንግሥት ውስጥ ጉልህ ሚና እንዲኖረው ጥረት የሚያደርጉ ቡድኖች አሉ። በተለይ ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ ወደ ዋይት ሐውስ የሚመለሱ ከሆነ ለዚህ አቋም አራማጆች ታላቅ ድል ነው። ከእነዚህም መካከል ትራምፕ “ከእግዚአብሔር የተላኩ ናቸው” ብለው የሚያምኑ እንዳሉ ሁሉ፤ ይህ እንቅስቃሴ ለአሜሪካ ዓለማዊ ፖለቲካ እና ዴሞክራሲ ስጋት ነው የሚሉ አሉ።