የትራምፕ ማሸነፍን በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውን እንዴት ይመለከቱታል? ለኢትዮጵያስ ምን ይዞ ይመጣል?
ከአራት ዓመታት በፊት በሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት የአፍሪካ አገራትን በማንቋሸሽ እና በጸያፍ ዘለፋዎች በመንቀፍ ይታወቃሉ ትራምፕ። “የአሜሪካን ታላቅነት በድጋሚ ለማምጣት” በተደጋጋሚ የሚምሉት ትራምፕ በፀረ-ስደተኝነት፣ በፀረ- ሙስሊም ንግግራቸው እና አቋማቸው ይታወቃሉ። ከሥልጣን ወርደው ለሁለተኛ ጊዜ በመመረጥ ታሪክ የሠሩት ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ለመሆኑ ትራምፕ ማሸነፋቸውን ኢትዮጵያውያን እንዴት ተመለከቱት?