ይህች ምድር የሁላችንም ናትና በኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር አለብን
ይህች ምድር የሁላችንም ናትና በኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት መፍጠር አለብን::
By Haile Mulu Dated: Sunday, 08 July 2012 00:00
አቶ ተሻለ ሰብሮ፣ የኢራፓ ፕሬዚዳንት
ምርጫ 97ን ተከትሎ በኅብረተሰቡ ዘንድ የተፈጠረውን ከፖለቲካ የመሸሽ ሁኔታ ለማስተካከልና ተስፋ የቆረጠውን ሕዝብ ተስፋ የማለምለም ራዕይ ሰንቆ መቋቋሙን የሚናገረው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ)፣ የተመሠረተበትን ሦስተኛ ዓመት በቅርቡ አክብሯል፡፡
የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል የሆነው ኢራፓ ሰሞኑን ለገዢው ፓርቲና ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት የብሔራዊ መግባባት ጥሪ አቅርቧል፡፡ አቶ ተሻለ ሰብሮ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡ ፓርቲው ባቀረበው የብሔራዊ መግባባት ጥሪና በሌሎች ተያያዥ አገራዊ ጉዳዮች ኃይሌ ሙሉ አነጋግሯቸዋል፡፡
ሪፖርተር፡- ኢራፓ ብሔራዊ መግባባት ያስፈልጋል የሚል ሐሳብ ይዞ መጥቷል፡፡ ብሔራዊ መግባባት ማለት ምን ማለት ነው? እንዴት ነው የሚገለጸው?
አቶ ተሻለ፡- በእንግሊዝኛው ብዙ ስያሜዎች አሉት፡፡ ‹‹National Reconciliation›› ይባላል፡፡ ‹‹National Dialogue›› ይባላል፡፡ ‹‹National Debate›› ይባላል፡፡ ብዙ ስሞች አሉት፡፡ የዚያን ቀጥተኛ ትርጉም ለመናገር ፈልገን አይደለም፡፡ በመሠረቱ ዓላማችን በሰላማዊ ትግል የተሻለችና የተሻሻለች ጠንካራ ኢትዮጵያን መመሥረት ከሆነ ከብሔራዊ መግባባት የተሻለ አማራጭ የለም፡፡ ወደድንም ጠላንም ወቅቱ የሚጠይቀን ይህንን ብቻ ነው፡፡
ብሔራዊ መግባባት ስንል ተራ እርቅ አይደለም፡፡ ተራ ሽምግልና አይደለም፡፡
ከዚህ ቀደም ብዙ ፓርቲዎች፣ ብዙ ግለሰቦችና ብዙ ጋዜጠኞች ብሔራዊ እርቅ ይደረግ ሲሉ ሰምተናል፡፡ ትክክል ናቸው፡፡ ነገር ግን ያ የመጨረሻ ምዕራፍ ነው፡፡ ከብሔራዊ እርቅ አስቀድሞ የኢትዮጵያ አጀንዳ በሚመለከታቸው አካላት መካከል ብሔራዊ ውይይት መጀመር አለበት፡፡ ብሔራዊ ውይይት ወደ ብሔራዊ መግባባት፣ ብሔራዊ መግባባት ደግሞ ወደ ብሔራዊ እርቅ ይመራንና ይደመደማል፡፡ የፖለቲካ ሰዎች፣ መሪዎች፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ግለሰቦችና የፕሬስ ሰዎች አንዱ በሌላው ላይ ሳይጠቁም፣ ጠርዝና ጠርዝ ይዞ የቃላት የጥላቻ ፖለቲካ ከማራመድ ባለፈ ተቀራርበው በአገሪቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ውይይት ማካሄድ አለባቸው፡፡ ክርክር ማካሄድ አለባቸው፡፡ ያ ወደ ብሔራዊ መግባባት ይወስደንና በሁሉም በአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ አካል ተፈጥሮ ብሔራዊ እርቅ የሚቀርጽ ሥራ ይሠራል፡፡
ሪፖርተር፡- ብሔራዊ መግባባትን አልፎ በቀጥታ ወደ ብሔራዊ እርቅ መግባት አይቻልም?
አቶ ተሻለ፡- አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ለብሔራዊ መግባባትም ሆነ ለብሔራዊ እርቅ የሚመች ሁኔታ አለ ወይ? ብለን መጠየቅ ይገባናል፡፡ ጊዜው እያለፈብን ነው፡፡ እንዲያውም የእኛ ስጋት 11ኛው ሰዓት ላይ ደርሰናል የሚል ነው፡፡ ዕድሎች እያመለጡን ነው፡፡
ሪፖርተር፡- አሥራ አንደኛው ሰዓት ላይ ደርሰናል ለማለት ያስደፈረዎት ምክንያት ምንድን ነው?
አቶ ተሻለ፡- አሥራ አንደኛው ሰዓት ላይ ምን ሊመጣ እንደሚችል ማየት አለብን፡፡ የአገራችን ነባራዊ ሁኔታዎች ምን ይመስላሉ ብሎ ማየት ያስፈልጋል፡፡ የፖለቲካ ቋንቋ አለ፡፡ ለምሳሌ ገዥው ፓርቲ አባላቱን ይገመግማቸዋል፡፡ በመስመር ውስጥ ናቸው አይደሉም? ተልዕኳቸውን ይወጣሉ አይወጡም? ብሎ ይገመግማል፡፡ እኛ ደግሞ በአገራችን ጉዳይ ላይ ኢሕአዴግ እንደ አንድ ባለቤትና ባለጉዳይ ሆኖ ሌሎች የፖለቲካ ሽኩቻዎችን ትተን ዜጐች፣ ምሁራን፣ የፕሬስ ሰዎች ሁሉም ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የውስጥ ተጨባጭ ሁኔታ መገምገም አለብን፡፡ ለምሳሌ በሃይማኖት ጥያቄዎች፣ በሰብዓዊ መብት አጠባበቅ፣ በዲሞክራሲ ጥያቄዎች፣ በኢንቨስትመንትና በአገር ልማት አካሄድና በመሳሰሉት አንኳር አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ወደ አንድ መግባባት መድረስ እንዳለበት የሚያሳዩ ጠቋሚ ምልክቶች አሉ፡፡ አዎ ልማት ይካሄዳል፡፡ ግን ልማቱ የሌሎችን ዜጐች ዲሞክራሲያዊ መብት የሚነካ ነው ወይስ አይደለም? ብለን መነጋገር አለብን፡፡ ልማቱን እንደግፋለን፡፡ ይህንን ልማት አብዛኛው ዜጋ የእኔ ነው ብሎ መቀበል አለበት፡፡ ዜጋው ዲሞክራሲያዊ መብቱና ተሳትፎው ሲረጋገጥለት ነው ልማቱ የእኔ ነው ብሎ የሚጠብቀውና የሚንከባከበው፡፡ ደርግ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ግድቦች ገድቦ ነበር፡፡ ደርግ በወደቀ በሰዓታት ልዩነት እነኛ ግድቦች ፈርሰዋል፡፡ ለምሳሌ ሀዲያ ውስጥ አንድ ቦታ ላይ ለምንም አገልግሎት በማይውል መሬት ላይ ልማት ይካሄድ ሲባል ሕዝቡ አልሳተፍም አለ፡፡ ደርግ ሲወድቅ በብዙ ሚሊዮኖች ወጪ የተገነባው ግድብ ፈረሰ፡፡ ጨለምተኛ ሆኜ ክፉ ነገር … (CONTINUED)
EDITORS NOTE: The information from this point forward is not in any way affiliated with Teshale Sebro. The information below is the view of the Brown Condor staff and editorial board and should not be taken as a continuation of Teshale Sebros’ message of the “Power of Reconciliation”.
HEBRET Circle
Petition Obama to Stop Supporting Meles Zenawi & TPLF
[click logo to sign change.org petition]
Those of you who are comfortable with putting your name behind the cause of seeing Meles Government fall, please sign the petition. This is not just to attempt to make a change. This is about standing together with your fellow Ethiopians in Solidarity. If we can’t sign a petition that takes a minute, what other change do we expect to make in our country or in our lives. If you believe that Meles TPLF regime should remain in power, please disregard this message.
CREDIT Circle
Organizer
Selam Ashenafi Mentire
[click to view profile]
Tsion Tesfaye
[click to view profile]
Click on either picture above and ask Selam or Tsion about their petition drive. We as Ethiopians cannot get things to change if we do not organize and petition the US government for relief and justice for our home Ethiopia.


