ዕውነትና ንጋት እያደር ይጠራል (የሽግግር ምክርቤት)

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሽግግር ም/ቤት የወጣ መግጫ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሽግግር ም/ቤት ያወጣዉን የአቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት የመለየት ዜና በተመለከተ ለመላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የገዢዉ ስርአት እንዲያረጋግጥ በፈጠረዉ ጫና መሰረት 24 ሰአት ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ ለመጀመርያ ጊዜ የስርአቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ እንደታመመ አምኗል። አቶ መለስ እንዳልታመመ ላለፉት በርካታ ሳምንታት ሲክድ የነበረዉ ስርአት አሁን ደሞ በመጠነኛ ህመም ላይ እንደሆነ ገልጾልናል። ለነገሩ 21 አመታት ሲዋሽ ለነበረ ስርአት መልሳቸዉ ባያስደንቅም አሁን ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ዝም ብሎ የሚያዳምጥበት ዘመን እንዳከተመ እናረጋግጥላቸዋለን። የሽግግር ም/ቤቱም አሁንም ስርአቱ በተጨባጭ በሶስተኛ ወገን የአቶ መለስን በሕይወት መኖር ለሕዝቡ እስካላረጋገጠ ድረስ አኛም ከራሳችን የታመኑ ም/ንጮች ያገኘነዉን የአቶ መለስን በህይወት ያለመኖር የሚያረጋግጥ መሆኑንና በኛም በኩል ከሃገር ደህንነት አኳያ እዉነቱ እስኪረጋገጥ ድረስ ጥያቄያችንን በህዝባችን ስም መጠየቃችንን እንቀጥላለን። ለኢትዮጵያ ህዝብ የምናስተላፈዉ መልእክት ሀገራችን ያለችበትን አስጨናቂ ሁኔታ በመገምገም በሀገር ደረጃ መደረግ ስለሚገባዉ ዝግጅት ባለዘጠኝ ነጥብ መግለጫ ማዉጣታችንን እያስታወስን በዚህ ወሳኝ ግዜ እዉነተኛ ህዝባዊ የሆነ መንግስት በድል እስኪመሰረት ድረስ ሀገር ወዳድ ዜጋ ሁሉ የተፈለገዉን መስእዋትነት እንዲከፍል ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የ ሽግግር ም/ቤት አመራር