አላሙዲ ያዘጋጀው የወያኔ ፌስቲቫልን ለማክሸፍ የተጠራ ሰልፍ – እሁድ 5 PM

ለሆዳቸዉ ያደሩ የአላሙዲ አሽከሮች AESAONE በሚል ስም ዋሽንግተን ዲሲ ያዘጋጁትን የወያኔ ፌስቲቫል ለመቃወም በተዘጋጀዉ ሕዝባዊ ሰልፍ ላይ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያነ ሁሉ እንድትገኙ እንጠይቃለን።

ሕጻናት በርሃብ ከሚቆሉባት ሃገራችን የተፈጥሮ ሃብትዋ በወያኔና አላሙዲ ሽርክና እየተበዘበዘ፣ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ለዋልጌዎችና ሆድአደሮች ያስረሽ-ምቺዉ ፌስቲቫል እየባከነ ነዉ። የዚህ ፌስቲቫል ዓላማ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈልና በገንዘብ ሃይል ለዘረኛዉ ወያኔ የዲያስፖራ ኢትዮጵያውያንን ድጋፍ ለመግዛት ነዉ።

በRFK Stadium በተዘጋጀው የተቃዉሞ ሰልፍ ላይ በመገኘት እነማ የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራና ስቃይ ችላ በማለት ለሆዳቸው እንዳደሩና ስብእናቸዉን ለገንዘብ እንደሸጡ ለይተዉ ይወቋቸዉ።

ቀን፡ እሁድ July 1, 2012.
ሰዓት፡ 5፡00 PM
ቦታ፡ RFK Stadium, Washington DC.