የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ መግለጫ

ከሃያ ሁለት ወራት ዝግጅት በኋላ፣ ከግንቦት 10 ቀን እስከ ግንቦት 13 ቀን 2004 ዓ.ም. (ሜይ 2012) ድረስ በካናዳ ዋና ከተማ በኦታዋ የተካሄደው ሁሉን አቀፍ የአንድነት ግንባር ምሥረታ ጉባኤ፣የልዩ ልዩ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ሲቪክ ማህበራትና ግለሰቦች ተሳትፈውበት በደረሱበት ስምምነት መሰረት “የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ” መመስረቱ የሚታወስ ነው። የሸንጎው አመራር ምክር ቤት ሥራውን በመጀመር የመጀመሪያውን መደበኛ ስብሰባ በግንቦት 20 ቀን 2004 .ም.(28-05-2012) አካሂዷል። በዚህ ስብሰባው የተለያዩ የሥራ ዘርፎችን የዘረጋ ሲሆን በእያንዳንዱ የሥራ ዘርፍ ውስጥ ገብተው የሚያገለግሉትን አባላት መድቧል። የስራ መመሪያዎችንም ሰጥቷል። በሀገራችን ያለውን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እንደገና ከዳሰሰ በኋላም አንዳንድ ውሳኔዎችን ወስኗል። … ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ