ወያኔ መውደቂያው ስለተቃረበ እንዳበደ ውሻ እየተቅበዘበዘ ነው
ከ አሰግድ ታመነ
የወያኔ መሪ መለሰ ዜናዊ በዘረፋ የተባበሩዋቸው ዘሮቻቸው ለግል ጥቅማቸውና ለሆዳቸው ሲሉ ህዝባቸውን ለባርነት አሳልፈው የሸጡ የሌላ ብሄር ተወላጆች ስለራሳቸው ጥቅም እንጂ ስለ ኢትዮጰያ ሕዝብና ብሄራዊ ጥቅም ምንም ግድ የሌላቸው መሆናቸውን እስካሁን የሰሩት እኩይ ተግባር በቂ መረጃ ነው:: ላለፉት 21 አመታትም የህዝብን ይሁንታ ሳያገኙ በጠመንጃ ሀይልና ወያኔ ኢትዮጵያን ካልገዛ ሀገሪቱዋ ትከፋፈላለች በሚል ማስፈራሪያ የስልጣንና የውንብድና እድሜያቸውን ከራሳቸው ጥቅምና ስልጣን ጋር እንደ ሰአት ቦምብ አስተሳስረው ኢትዮጵያን ፍፁም ወደሆነ አምባገነን ስርአት አዘቅት ውስጥ ከተዋታል። የወያኔንና የሎሌዎቹን የውንብድና የህዝብና የሀገር ሀብት ዘረፋ እድሜ ለማራዘም እያሉ ኢትዮጵያዊያንን በተለያዩ ምክንያቶች በመከፋፈልና እርስ በእርሳቸው እንዲበጣበጡ ሲያደርጉ ቆይተዋል። እስካሁን ወያኔ በስልጣን ላይ የቆየው በፈጠረው ህዝብን በብሄር: በሀይማኖት: በቋንቋ: በጎጥ: በአናናር ዘይቤው: ከቀድሞ ስርአቶች ጋር በነበራቸው ትስስር ወዘተ መከፋፈልን በመፍጠር በጋራ ተባብረው ከወያኔ የበለጠ ሀይል እንዳይፈጥሩ በማድረግ ነበረ::
የህንንም የመከፋፈል ሴራ ተጠቅሞ ወያኔ በስልጣን ላይ መቆየት የሚያስችለውን ድርጅትም ሆነ አባላትን መመስረትና ማሰባሰብ አልቻለም:: ለዚህም ትልቁ ምስክሮቹ እራሱ ወያኔ የበሰበሰ የገማ ምናምን እያለ እስካሁን ድረስ ያካሄዳቸው ድርጅታዊና አቁዋማዊ ተሀድሶዎች; የአባላቶችና የደጋፊዎች በጥቅም የመተሳሰር; የህዝብና የሀገር ሀብት ዘረፋና ሙስናና ብልሹ አሰራር ናቸው:: አሁን ወያኔ ልክ እንደሱ በብሄር ደረጃ ከተደራጁ ፓርቲዎች ጋር እንኩዋን የመፎካከር አቅም የለውም ስለዚህ እያደረገው ያለው ተቃዋሚዎች ከወያኔ ያነሰ ድርጅታዊ አቅም እንዲኖራቸው ማድረግ ነው ለዚህም እኩይ ተግባሩ እያደረገ ያለው ህዝቡን በትንንሽ ቡድኖች እንዲደራጁና ከወያኔ ያነሱ እንዲሆኑ ማድረግ ነው:: የወያኔ ቡድኖችን የመከፋፈል ተግባሩ ሰሞኑን በሙስሊም ማህበረሰብ ላይ አነጣጥሮዋል::
በአወሊያ ትምህርት ቤት አስተዳደር ጉዳይ የተለኮሰው የሙስሊሞች ተቃውሞ በአዲስ አበባ በደሴ በከሚሴና በአሳሳ እየተቀጣጠለ እዚህ ደርስዋል። መረጃዎች እንደ ሚያሳዩት ከሆነ ሙስሊም ምእመናን በአወሊያ ትምህርት ቤት ና በአንዋር መስኪድ በየሳምንቱ ዓርብ የሚያደርጉት ተቃውሞ ወራትን አስቆጥሯል። ከዓርብ የጁምአ ስግደት ጋራ ተያይዞ በሚደረገው በዚህ የተቃውሞ ስብስብ ጎልተው የወጡት ተቃውሞዎች “የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤቱን” (መጅሊሱን) አመራርና አሠራር እንዲሁም የመንግሥትን ጣልቃ ገብነትን የሚመለከቱ ናቸው። ተሰብሳቢዎቹ “አባይ ይገደባል፣ መጅሊስ ይወገዳል” የሚሉ መፈክሮችን ሲያሰሙ መሰንበታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል። “መጅሊስ አይወክለንም” “መሪዎቻችንን መንግሥት ሳይሆን ራሳችን እንምረጥ” የሚሉ ጥያቄ አዘል መፈክሮችም በስፋት ያሰሙ ሲሆን ተቃውማቸውንም በዚምታ አፋቸውን በ ፕላስተር በ መለጠፍ የገለጡበት ሁኔታም ነበር። በዚህም ተቃውሞ ፍርዶስን ጨምሮ ስድስት ሙስሊም ምእመናን ተገለዋል በርካቶች እስርና ድብደባ ደርሶባቸዋል።
ሌላው የተቃውሞ ምንጭ መንግሥት በሙስሊሙ ላይ “አህበሽ” የሚባለውን አስተምህሮ ለመጫን ያደርገዋል በተባለው ጫና ላይ ያነጣጠረ ነው። ከወራት በፊት መንግሥት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች “አሕበሽ” የተባለውን አስተምህሮ እንዲቀበሉ ጫና ለማድረግ መጀመሩና ይህም በርካታ የሃይማኖቱን ተከታዮችና ሌሎችንም ታዛቢዎች ማስቆጣቱ ይታወሳል።
በአዲስ አበባ may 16 ታትሞ የወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ በአማራ ክልል በላሊበላ የሚገኙ የሙሉ ወንጌል አማኞች ለአምልኮ የሚገለገሉበት ቤት ካለፍርድ ቤት ታሸገ ዜና አስነብቧል። በዚህም ወያኔ ፊቱን ወደ ፕሮቴስታንት በማዞር የአምልኮ ቦታቸውን ማሸግ ሌላ አጣብቂኝ ውስጥ ክቶታል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በኩል ደሞ ወያኔ በሰሜኑ ሀገራችን ክፍል በሚገኘው ታላቁ የዋልድባ ገዳም አካባቢ የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ ግንባታ፣ የፓርክ ይዞታ፣ እንዲሁም የመንገድ ጥርጊያ እሰራለሁ በሚል ሰበብ የዋልድባ ገዳም ይዞታን የተለያዩ ከባድና ቀላል የእርሻ መሳሪያዎችን በመጠቀም አጽመ ቅዱሳንን በማፍለስ፣ ቦታውንም በዶዘር በማረስ መጠነ ሰፊ የሆነ የጥፋት ዘማቻ ከጀመረ ውሎ አድሯል፤ ቦታው የመድኃኒዓለም ስም የሚወደስበት የሚሰለስበት ቅዱስ ቦታ ነው ያሉ ገዳማውያኑም ምህመናንም አቤቱታቸውን ቢያሰሙም ተቀባይነት ባለማግኝታቸው ከጎንደር ሕዝብና ከምሕመናን ጋር ጥርስ እንዳናከሰውና እንደ ተፋጠጡ እስካሁን አሉ ።
በእውነቱ ከሆነ ከወያኔ የተረፈን ነገር ቢኖር
1- አለመተማመን
2- ታሪክ መበረዝ
3- አባቶችን መስደብ
4- ደመኝነት
5- ዘረኝነት
6- መሬታችንን በመሸጥ በአገራችን ሁለተኛ ዜጋ መሆን
በዚህም ምክንያት በየጊዜው ለድርቅና ረሀብ ለግጭትና ለመከራ ሲዳርጉን ህነዚህ የወያኔ መሪ ታሪካችንን እያጠፉ ከብሔር ብሔር ከጎሳ ጎሳ ከሃይማኖት ሃይማኖት እያጋጨ የትግራይን ሕዳሴ በማፋጠን ላይ ይገኛሉ፡፡
በመላው አገራችን እየተፈፀመ ላለውና ቀደም ሲል ለተፈፀሙት ኢሰብዓዊ ተግባር እዲሁም ታላቅዋ ትግራይ ለመመስረት እያደረሱ ያሉት ሌላውን በዘር የማጨፋጨፍ እንቅስቃሴ ከአቶ መለስ ጀምሮ ራሱን “በነጻአውጪ ግምባር” ስም ሰይሞ ኢትዮጵያን እየገዛ ያለውን ህወሃት/ኢህአዴግን፣ እንዲሁም በተዋረድ እስከታች ድረስ ትዕዛዝ ፈጻሚ የሆኑትን ሁሉ በቀጥታ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል፡፡