እድር የረሳው ሬሳ – ለሰሎሞን ተካልኝ

ከጋቹዬ አቹሌ

ምን ፈርስ ቢነፋው -ሆዱን እንደ ኩንታል፣
ሰው እንዴት በቁሙ-እንደዚህ ይሸታል?

ምን ዶማ ራስ ቢሆን -ከዲንጋ’ ማይሻል፣
ሰው እንዴት በሜዳ -ብስና ያቀረሻል?

ምን የጅል ጅል ቢሆን -አጎዛ ሙሀቻ፣
እንዴት ሰው ይሆናል – ዕቃ መጫዎቻ?

ምን ሆዱ ቢሰፋ -ከምንቸት ከቶፋ፣
እንዴት ነው በአፉ – ሰው ንፍጥ የሚተፋ?

ምን ቆለጥን ቢሆን – ሁልጊዜ አጨብጫቢ፣
እንዴት ሰው ይሆናል – የሰው ካካ አጣቢ? …

እያልኩኝ ስገረም – ነገሩን ሣስሰው፣
ለካ ሰው አይደለም -ሙት ነው የምወቅሰው።

በቁሙ የሞተ-ዳግም ላይነሳ፣
እድሩ ሳይቀብረው – የረሳው ሬሳ።