የአንበሳ ባንክ አዲሱ ቦርድ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ተቃውሞውን አቀረበ

(በውድነህ ዘነበ)

የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አካሂዶት የነበረውን የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ የሕግ ስህተት ያለበት ነው በሚል፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውድቅ ማድረጉን አዲስ የተመረጠው የአንበሳ ባንክ ቦርድ አጥብቆ ተቃወመ፡፡