ከዝንብ ማር አንጠብቅም

ሚሊዮን ጎሣዬ (ከኦስሎ – ኖርዌይ)

አይሆንም እንጂ ቢሆንና ዝንብ ማር መስጠት ብትጀምር ከአዲስ አበባ አካባቢዎች እንደ ተክለኃይማኖትና መርካቶ ማርን በብዛት የሚያመርት ይኖራል ብዬ አልገምትም። ለምን? ቢሉ አዲስ አበባ ምን ትላለች እኔም አፍንጫ የለኝም ነው ያለው ጋሽ ስብሃት። እውነታው ግን ዝንብም ማር ሰጥታ አታውቅም፤ ወያኔም ዴሞክራሲያዊ ምርጫን።