የሌ/ኰ መንግሥቱ ኃይለማሪያም መጽሐፍ በኦፊሴል ነገ ገበያ ላይ ይውላል

L.Colonel Mengistu H.Mariamበዛሬው ዕለት ገበያ ላይ የዋለው ሁለት ሺህ ቅጂ በአንድ ሰዓት ውስጥ አለቀ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሐምሌ 16 ቀን 2002 ዓ.ም. July 23, 2010)፦ በጋዜጠኛና ፀሐፊ ገነት አየለ የተዘጋጀው ”የሌተና ኰሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ትዝታዎች (ቁጥር 2)” መጽሐፍ ነገ ቅዳሜ ሐምሌ 17 ቀን 2002 ዓ.ም. (ጁላይ 24 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በኦፊሴል ገበያ ላይ ይውላል። ዛሬ ማምሻውን በጥቂቱ ለሽያጭ የቀረበው ሁለት ሺህ ቅጂ በአንድ ሰዓት ውስጥ ተሸጦ ማለቁን ከአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ሪፖርተር ዘግቧል።