አቡነ አብርሃም ወደ አዲስ አበባ የሂዱበት የተጨማሪ ኢጲስ ቆጶስነት አስመራጭ ኮሚቴ ስለሆኑ ነው

Image may contain: 1 person

የዘመናችን አቡነ ጴጥሮስ የምእራብ ጎጃም ዞን እና የባህር ከተማ ሊቀ ጳጳስ አቡነ አብርሀም በመስቀል በአል ላይ በግልፅ የህዝብ አባት መሆናቸውን ካሳዩ በኋላ በካድሬው አባት ተብዬ ተጠረተው ወደ አዲስ አበባ መግባታቸው መነገሩ ይታወሳል። ሆኖም አባታችን አቡነ አብርሃም ወደ አዲስ አበባ የሂዱበት ዋና ስራ የተጨማሪ ኢጲስ ቆጶስነት አስመራጭ ኮሚቴ ስለሆኑ እና የተመለመሉ አባቶችን የመጨረሻ ውጤት ለጥቅምቱ አጠቃላይ የሲኖዶስ ስብሰባ ለማድረስ እንደሆነ እና እስካሁን በተናገሩት ታሪካዊ ንግግር ዙሪያ ማንም ምንም ለማለት እንዳልሞከረና እንዳልደፈረ ለአባታችን ቅርብ የሆኑ ሰዎች መረጃውን አድርሰውናል።
እረጅም እድሜ እና ጤና ለእውነተኛ የበጎች እረኛ ለሆኑ አባታችን አቡነ አብርሃም።