“እንዳትረግጡት…. የኢትዮጵያን ዐፈር- መሬት! ”

ባካችሁ ……… ’ባካችሁ……….

እናንት  በምድረኢትዮጵያ  ያላችሁ፤

አትሂዱ …..ግራችሁ…”

ከቻላችሁ ….. “ብረሩ  ክንፍ  አውታችሁ።

ግን…….. አደራ……….. ……….

አንዳትረገጡት …….  መሬቱን

እንዳታዩት………  አፈሩን፤

ብታርሱት…… አትዘሩበት

ብዘሩበት …….. አይበቅልበት፤……..

ደም  ነውናየትላንናየዛሬየአሁን፣ ትኩስ…. የፈሰሰበት

አጥንት ነውና   ያልደረቀ አጸደህይወትየወደቀበት

 እናንተም  ከእንግዲህ ፣ ”ዐጽም – ‘ርስቴ” የማትሉት፤………..

ያውም ………………………………..

 የባቶቻችሁ፣…….. የናቶቻችሁ

ያውም………………………………

የወንድሞቻችሁ፣……..  የህቶቻችሁ

ያውም……………………………………

የእቦቀቅላወቹ፣……  የታዳጊወቹ፣……..የልጆቻችሁ፤

 ዓይናችሁ  እያየ፣……. እየሰማ   ጆሮችሁ

የተመቱ! … የቆሰሉ!….. የተወጉ! …. የተፈነከቱ!…..

የተቀጠቀጡ!….  የተዘለዘሉ!……! ……የተረሸኑ!

….. በገዛ   ወገኖቻችሁ………..

ያውም …………”ወገን እኮ  ነን “ እያላችሁ።

በደመዋ   ልባችሁ……………………………….

 “ኤሉሄ …..ላማ ሰበቅተኒ!”……. ብላችሁ

 ወሰንድንበር  ለሌለው   ሰቆቃችሁ

ብትነግሩትም   “ለሰማይ   አባታችሁ”፤

ግን….. ለምንም –  ለማንም   አይመችም

ሀዘናችሁ   መልክ   የለውም……….

ያልተነገረ  እንጅ፣ ያልተፈጸመባችሁ   ግፍ  የለም።

ብትጎጉጡ፣ ደም  አልቅሳችሁ፣…..  እየየብላችሁ

ቢያዳርስም   ዓለም  …..  ሲቃዋይታችሁ

መቼምመቼም  ቢሆን፣ ምንጩ   አይደርቅም   ምባችሁ::…..

እናማ………………………………………..

ሰላም፣ ፍትህ፣ እኩልነትሳታሰፍኑበመሀከላችሁ

አንድነትን  ሳታነግሱ  –  በምድራችሁ

ይቅር  ሳትባባሉ፣  ‘ርስ በርሳችሁ

ሳይመለስ  ክብራችሁ፣  ጠፈር –  ድንበራችሁ

የድል  ችቦው –  ከፍ  ሳይል ክብር  ሰንደቅ  ዓላማችሁ፤……

የወገናችሁን  ደምናአጥንት  እንዳትረግጡት

ይወጋችሁልና   እሾኽ  ሆኖ፣  የኢትዮጵያ    ዐፈርመሬት!

 ———//———

ፊልጶስ/ ነሀሴ 2008

E-mail: [email protected]