እሳት ነው ወጣቱ።
እሳት ነው ወጣቱ።
ከአቢይ ኢትዮጵያዊ ሥጋዊ ወ-መንፈሳዊ
እሳት ነው ወጣቱ።
እየለበለበ፤
እያንገበገበ፤
ጠላት ያነደደ፤
ባንዳዎች ያጨደ::
ሐቅ ነው ከጥንቱ፤
አያውቅም ብላችሁ እንዳትጫወቱ፤
ይፋጃል በደሙ እሳት ነው ወጣቱ::
እንኳን ላገራችን፤
ለነፃነታችን፤
ይረ-ሳል መገ ደል?
ይበልጥ በወቸገል??
ስንቱ ጀግና ወድቋል፤
በአጋዚ ሕዝብ አልቋል::
ጅቦች እየመራ፤
ለወገን ሳይራራ፤
ራሱ ጅብ ሁኖ፤
በቅንድብ ሸፍኖ፤
እሱም እየበላ፤
ባዕድ ጅብ ሲያበላ፤
ሃያ ዓመታት ሆነ፤
ደም ከተጀቦነ ::
መለስ ነው “ወቸገል”፤
የሚገል የሚያስገ’ል።
ሌላው ፍርፋሪ ሊጠርግ የተሸጠ፤
ሥልጣን ያራዝማል እያበጣበጠ::
አገር ሁሉን ያውቃል፤
ያን ቀን ይጠብቃል::
ቢሆንም ይጀመር ሌላውም አይቀርም፤
እያንዳንዱን ባንዳ ወጣቱ አይምርም::
እየለበለበ፤
እያንገበገበ፤
ጠላት ያነደደ፤
ባንዳዎች ያጨደ፤
ሐቅ ነው ከጥንቱ፤
አያውቅም ብላችሁ እንዳትጫወቱ፤
ይፋጃል በደሙ እሳት ነው ወጣቱ ::
በግፍ እንደታሰረ፤
ነብስ እየገበረ፤
ደም እንደከፈለ፤
በአምባገነኖቹ እየተገደለ፤
ዛሬም ይታገላል ከሕዝቡ ውስጥ አለ::
ሕዝቡም እያወቀ አምርሮ ተነስቷል፤
ሰበብ ነው የቀረው ትዕግስቱ አብቅቷል::
እናም ነፃነት እንበል፤
ቆርጠን እንታገል፤
ከመለስ ካልጀመርን፤
በግል ካላመረርን፤
ወያኔ ጎናችን መግደል ይቀጥላል፤
መጪው የእኛ ትውልድ:-
ብዙ ደም ይከፍላል::
ግና ዛሬ መለስ፤
የበላው እስኪመለስ፤
እጁ ይያዝ የታል??
ጀግናው መጥቶለታል፤
“ወቸገል”እሱ ነው፤
መግደል የተካነው ::
እናም ይያዝ የታል??
በቃ አልቆለታል::
የሚለበልበው፤
የሚያንገበግበው፤
ፍሞ የሚያነደው፤
ባንዳዎች ያጨደው::
ሰበቡን ጠብቆ፤
የሚገለው አንቆ፤
መጋሙ ሲጀምር፤
ሕዝብ ሲነሳ የምር፤
አይምርም ከጥንቱ፤
አያውቅም ብላችሁ እንዳትጫወቱ፤
ይፋጃል በደሙ እሳት ነው ወጣቱ::