የምሥራች! ትግርኛና አማርኛም በላቲን ፊደል ሊጻፉ ነው
ይሄይስ አእምሮ

መምህር ልዑለቃል አካሉ የተባሉ ኢትዮጵያዊ በቅርቡ በኦሮምኛ ቋንቋ የላቲን ፊደል አጠቃቀም ዙሪያ የጻፉትን መጣጥፍ ቆየት ብዬም ቢሆን ዛሬ አነበብኩት፤ ግሩም ነው። እሳቸው የሚሉት “ለኦሮምኛው ከላቲን ይልቅ የግዕዙ ፊደል አይቀርብም ወይ?” ነው። ይሄን ያህል ለምን ሩቅ ተሄደ ነው ጥያቄያቸው። ላቲኑን ለመጠቀም ለምን ያን ያህል ሩቅ መንገድ መጓዝ እንዳስፈለገም መልሱ በመጣጥፉ ውስጥ አለ – ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች በወያኔ በመታገዝ ሀገሪቱን ለመበታተን ከሸረቡት ሤራ አንዱ መሆኑ በስፋት ተጠቅሷል።