የድምፃዊት አለም ከበደ አስራ አንድ አመት የፈጀ የሙዚቃ አልበም – VOA

አለም ከበደ ለየት ባለው የአዘፋፈን ስልቷ ትታወቃለች። ከሙዚቃ ህይወት ባትርቅም አዳዲስ ስራዎች ለአድማጭ ለማቅረብ ግን ረጅም ጊዜ ወስዶባታል። የዘፈነቻቸው ዜማዎች በተለይም ‘አተረማመሰው’፣ ’በለው በለው’ እና ‘አራዳ’ የተባሉት ዜማዎች በአድማጭ ተወዳጅ በመሆናቸው በተለያዩ የኢትዮጵያ ድምፃውያን ዘንድ ተደጋግመው ተዘፍነዋል። ከዚህ ቀደም በሰራቻቸው ሦስት የሙዚቃ አልበሞች በርካታ አድናቂዎችን አትርፋለች ባሳለፍነው ወር መጨረሻ አራተኛዋ የሆነውን አዲስ የሙዚቃ አልበም ለአድማጭ አቅርባለች። አለም ከበደን በአዳዲስ ስራዎች ቶሎ ቶሎ ያላየናት ለምንድነው? በሙዚቃ ህይወቷ ዙሪያ ከመስታወት አራጋው ጋር አጭር ቆይታ አድርጋለች። ያዳምጡ → listen