በደሴ እና በአቅራቢያ ከተሞች የአሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ እየተደረገ ይገኛል::
በደሴ እና በአቅራቢያ ከተሞች የአሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ እየተደረገ ይገኛል::
#Ethiopia #Dessie #TaxiDriversStrike #MinilikSalsawi #Freedom #Change

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ከወሎ ክፍለሃገር የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በደሴ እና አከባቢው ከተሞች የአሽከርካሪዎች የስራ ማቆም አድማ እየተደረገ ይገኛል::የወያኔ ፖሊሶች እና ካድሬዎች ታርጋ እየፈቱ ቢገኙም ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው::በዚህም መሰረት ደሴ ከ4 መቶ የማያንሱ ታክሲ እና ከ 3 መቶ በላይ ባጃጆች አሏት ዛሬ ጥቂቶች ናቸው የሰሩት አድማው ከሰአት ቡሀላ ተተናክሮ ይቀጥላል ተብሏል በሚሰሩ መኪኖች ላይ እርምጃም እንወስዳለን ብሏል ህዝቡ::
ከአሽከርካሪዎች ጋር በመተባባር እርምጃው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ነጻነት የናፈቀው የደሴ የወልዲያ እና የአከባቢው ከተሞች ሕዝብ ከአሽከርካሪዎች ጎን መቆሙን በተግባር አሳይቷል::በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ከአሽከርካሪዎች ጋር በተያያዘ የወያኔ አገዛዝ ከፍተኛ የሆነ የመብት ገፈፋ እንደሚያካሂድ የታወቀ ሲሆን የትራፊክ ፖሊሶች በዘረፋ ላይ መሰማራታቸው በተደጋጋሚ እየተነገረ ይገኛል:: የአዲስ አበባ የታክሲዎችን አድማ ተከትሎ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል ከፍተኛ የሆነ መተባበሮች እና አድማዎች ቀጥለዋል:: #ምንሊክሳልሳዊ


