የኦሕዴድ ዉሳኔ፤ ድጋፍና ተቃዉሞዉ

በኦሮሚያ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሐላፊ እንደሚሉት ዕቅዱን ሕዝቡ፤ በእሳቸዉ አገላለጥ «ከጫፍ እስከ ጫፍ» ተቃዉሞታል።በማስተር ፕላኑ ሰበብ በተነሳው ተቃውሞ በሁለት ወራት ጊዜ ዉስጥ ወደ 140 ሰዎች እንደተገደሉ ና በርካቶች እንደቆሰሉ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በምህፃሩ ኦፌኮ አስታውቋል