መፍትሄ ያላገኘዉ የኢትዮጵያና የኤርትራ ዉዝግብ

በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የቀጠለዉ ቁርቁስና፣ ፖለቲካዊ ዉዝግብ አሁን ደግሞ በስፖርቱ ላይ ጫናዉን ያሳረፈ መስሏል። ኢትዮጵያ ከሕዳር 11 ጀምሮ ለ 15 ቀናት በምታስተናግደዉ የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሀገሮች «ሴካፋ» የእግር ኳስ ሻምፒዮናን ኤርትራ እንዳትካፈል ኢትዮጵያ አግዳለች ሲል አሶሺየትድ ፕረስ ያወጣዉን ዘገባ ተከትሎ፤