የጀርመን ሬድዮ ስለምርጫው ከሶስት ጋዜጠኞች ጋር ያደረገው ውይይት (+Audio)
የጀርመን ሬድዮ አማርኛ አገልግሎት አምስተኛውን ዙር የፌዴራልና የክልል ምርጫ በተመለከተ ከሶስት ጋዜጠኞች ውይይት አድርጎ ነበር። የራዲዮ ጣቢያው ጋዜጠኛ ሂሩት መለሰ፡- ከየማነ ናግሽ (ሪፖርተር ጋዜጣ)፣ ከ.ይልማ ኃ/ሚካኤል (የጀርመን ሬድዮ የበርሊን ወኪል) እና ከገበያው ንጉሴ(የጀርመን ሬድዮ የብራስልስ ዘጋቢ) ጋር፤ ስለቅድመ ምርጫውና ድምፅ የተሰጠበት ሂደትና ውጤቱ እንዲሁም የወደፊት ዕጣፈንታና የውጭ ኃይሎች ሚና አስመልክቶ ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱ ከተነሱት መህል፡- 1/የማነ ናግሽ (ሪፖርተር ጋዜጣ):- *የተቃዋሚ ተወካዮች እንዳይታዘቡ ተከልክለዋል። ውጤቱ ለጥርጣሬ ክፍት ያደርጓል። *አባሎቻቸውን ገለልተኛ ታዛቢ ሆነው የቀረቡት የአገርውስጥ ማህበራት የፓለቲካ ድጋፍ እንዲሰጡ የተደራጁ እንጂ ገለልተኛ አይደሉም። *የውጭ ኃይሎች ላይ መንጠልጠል ጥገኛ አስተሳሰብ ነው። የጉዳዩ ዋና ባለቤት ህዝብ ነው። ህዝቡ ድምፄን ተሰርቋል ብሎ ካመነ እስከመቼ(ለምን) ቁጭ ብሎ ያያል? *ተቃዋሚዎች በራሳቸው ለማሸነፍ አልገቡም። ተበታትነውና ዓቅመቢስ ሆነው ነበር የቀረቡት። አንድም ተቃዋሚ በተወዳደረባቸው ቦታዎች በሙሉ ቢያሸንፍ መንግስት ለመመስረት የሚችል አልነበረም። * በእኛ ዓይነት ብዝኃ-ህብረሰብ ውስጥ በዚህ ደረጃ ማሸነፍ አይቻልም። አንድም ድርጅት እንዲህ ዓይነት የአስተሳሰብ አንድነት መፍጠር አይቻለውም። ውጤቱ ለኢህአዴግ አስደንጋጭ እንጂ መልካም ነገር አይደለም።ድርጅቱ ያየዘው አቋም መፈተሽ አለበት። *ተቃዋሚዎችን በማድቀቅ ሳይሆን ሜዳውን ክፍት አድርጎ በተሻለ አስተሳሰብ ለመብለጥ መስራት አለበት። *ነገሩ ሂዶ ሂዶ ወዴት እንደሚያደርሰን አይታወቅም። —– 2/ ይልማ ኃ/ሚካኤል (የጀርመን ሬድዮ የበርሊን ወኪል)፡- *ማን አሸናፊ ሆኖ እንደሚወጣ ሳይታለም የተፈታ ነበር። *የሸንጎ ምርጫ ከኳስ ጨዋታ ጋር እኩል ነው። ገለልተኛ ዳኛና ሜዳ በሌለበት አይደረግም። *ተቃዋማ ፓርቲዎች ምንም ተስፋ አልነበራቸውም። *ዕርዳታ ሰጪ […]