ህወሃት ስለሃለማርያም የቤት ስራውን ጨርሷል ተባለ

ሃይለማርያም ከስልጣን ሲባረር እ አ አቆጣጠር በ2009 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጥቅምና ምቾት ለመወሰን የወጣው አዋጅ ለሃይማርያም የማያገለግልና ሃይለማርያም የዚህ ተጠቃሚ እንደማይሆን ታውቋል።

ሃይለማርያም ከስልጣን ሲባረር እ አ አቆጣጠር በ2009 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጥቅምና ምቾት ለመወሰን የወጣው አዋጅ ለሃይማርያም የማያገለግልና ሃይለማርያም የዚህ ተጠቃሚ እንደማይሆን ታውቋል።
ቀደም ብሎ ህወሃት ሃይለማርያምን ለማስወገድና የህወሃቱን ቴድሮስ አድሃኖም ጠ/ሚንስቴር አድርጎ ለመሾም መስማማቱን ዘግበን ነበር።

አሁን ደግሞ የደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ሃይለማርያም ስልጣኑን ሲለቅ ከስልጣን ለተገለሉ ለከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የሚደረገው ጥቅምና እንክብካቤ ሊደረግለት እንደማይገባ ህወሃቶች ተስማምተውበታል፡
ለዚህም ያዘጋጁት ምክንያንያት

1ኛ. በProclamation No. 653/2009 አንቀጽ 12. Pension Rights ንኡስ ቁጥር
“1/ Notwithstanding any provision to the contrary under the relevant pension law, if a Senior Government Official who has served for at least one election term:”
አንድ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ቢያንስ የአንድ የምርጫ ዘመን ማገልገል አለበት የሚለውን እንደሚጠቅሱበትና እሱ ደግሞ ይህን ስለማያሟላ ጥቅማ ጥቅሙ አይገባውም። ዳግመኛም እንደማይመረጥ ተወስኗል፤ እንዳውም በምርጫ ጣቢያው በሌላ ተወዳዳሪ እንሚሸነፍ ይጠበቃል፡

2ኛ. ጥቅሙ የሚገባው በረሃ ለታገሉ እንጂ እዚህ ከተማ ተቀምጠው ከድል በሗላ ብቅ ለሚሉ መሆን የለበትም የሚሉ አክራሪ የህወሃት አባላት ለመቶ አለቃ ግርማ የሚደረገው እንክብካቤም ስህተት መሆኑንና እንደሚያንገበግባቸው ተገልጿል፡
ባለራዕዩ መሪ መለስ ዜናዊ በህይወት ኖሮ ያላገኘውን እንክብካቤና ክብር ሃይለማርያም ሊያገኝ አይገባም የሚሉም አሉ፡ ሃይለማርያም ስልጣን ከለቀቀ በሗላ የመለስን ስም የሚያገዝፍ የሃይለማርያምን ደግሞ የሚያቀጭጭ ዶክመንታሪ እንደሚሰራ፡ ዶክመንታሪውም የሃይለማርያም ንግግሮች እየተቀነጨቡ ምን ያህል ብቃት የለለው እንደነበርና እሱን መጀመሪያውኑ ስልጣን ላይ ማስቀመጥ ስህተት እንደነበር የሚዘረዝርና ባንጻሩ መለስ ዜናዊ ካደረጋቸው ንግግሮች ተመርጠው እንደሚካተቱና ምን ያህል ብልህና ባለራዕይ መሪ እንደነበር በንጽጽር እንደሚቀርብ ይጠበቃል።

ሰሞኑን ሃይለማርያም ላይ የተደረገው 15 ሰዓት የፈጀና ከላይ እስከታች እንዲተቹት የተደረገው በህወሃት አቀናባሪነት የዚህ እቅድ አካል እንደሆነ የውስጥ አዋቂ ምንጮት ይገልጻሉ፡ ከግምገማው በሗላ አሁንም ስህተቱን ለመቀበልና ለመማር ዝግጁ አደለም የሚሉት ትችቶች ሳጥኑ ላይ የመጨረሻው ምስማር መሆኑን ያመለክታል።