የየመን ወቅታዊ ሁኔታና ኢትዮጵያውያን

በሣዑዲ ዐረቢያ መራሹ የአየር ጥቃት የመን ውስጥ የተከፈተው ዘመቻ ስድስተኛ ቀኑን ባስቆጠረበት በዛሬው ቀን ከ40 በላይ ስደተኞች መገደላቸውን 65 መቁሰላቸውን የየመኑ ወኪላችን ገለጠ። የዓለም አቀፍ ስድተኞች ድርጅት (IOM) በማነጋገር ያገኘሁት ነው ባለው መረጃ መሠረት ከሟቾቹ መካከል ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል ።