ሰማያዊ ፓርቲና ሰላማዊ ሰልፎቹ

ሰማያዊ ፓርቲ፣ ትናንት በ 15 የተለያዩ ከተሞች ሊያካሂድ ያሰበውን ሰላማዊ ሰልፍ ከ 4 ከተሞች በስተቀር በፖሊስ መደናቀፉን የፓርቲው ሊቀመንበር ገለጡ። አዲስ አበባ የተጠራዉ ሰልፍ በታቀደዉ መንገድ መሄድ ባለ መቻሉ ተቃዉሞ ሰልፉ ከጽ/ቤቱ ብዙም ሳይርቅ መደረጉ ተመልክቶአል