ሽብር በቱኒዝያ፥ «የእሥላማዊ መንግሥት» መስፋፋት
ዱካውን በአፍጋኒስታንና ፓኪስታን አሳርፎ ሰሜንና ምዕራብ አፍሪቃ መድረስ ችሏል። ከናይጄሪያው ሌላኛው አሸባሪ ድርጅት ቦኮሃራም ጋር መወዳጀቱ፣ በሊቢያ መንሰራፋቱ ይነገርለታል። አሸባሪው ቡድን በሊቢያ የግብፅ ኦርቶዶክሶችን አንገት ለካራ መዳረጉ የቅርብ ትዝታነቱ ገና ሳይዘነጋ፤ በደም የታጠበ እጁን በንዑሷ ቱኒዝያ ለተጨማሪ ጥፋት መዘርጋቱ አልቀረም።