የስፖርት ዘገባ፤ መጋቢት 14 ቀን፣ 2007 ዓ.ም

ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች በሮም ማራቶን በወንድም በሴትም አሸናፊ ሆነዋል። በጀርመን ቡንደስ ሊጋ የዘንድሮ ውድድር ባየር ሙይንሽን በሜዳው ለመጀመሪያ ጊዜ ሽንፈት ገጥሞታል። በስፔን ላሊጋ ባርሴሎና ዋነኛ ተፎካካሪው ሪያል ማድሪድን አሸንፏል። የሊቨርፑሉ ሽቴፋን ዤራርድ ከሜዳ በቀይ ካርድ ተሰናብቷል።