ሰበር ዜና:- በአሰቦት ገዳም ደን ላይ የእሳት ቃጠሎ ተቀሰቀሰ

asebotየወያኔ ዘመቻ በገዳማት ላይ ቀጥሏል

በዛሬው እለት ረፋድ ላይ ከገዳሙ በስተሰሜን አቅጣጫ የተቀሰቀሰው እሳት ማኅበረ መነኮሳቱ አና ከመኢሶ ከተማ ከመጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት ጋር እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ተደርጓል፡፡ ነገር ግን በሌላ አቅጣጫ ከገዳሙ ደን በቅርብ ርቀት እሳቱ እየተቀጣጠለ እንደሚገኝ ከገዳሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በስተሰሜን አቅጣጫ የተነሳው እሳት በማኅበረ መነኮሳቱ እና የፌደራል ፖሊስ አባላት ለማጥፋት ጥረት የተደረገ ቢሆንም ጭሱ ግን አሁንም እንዳለ በስልክ ያነጋገርናቸው የገዳሙ መነኮሳት ገለጸዋል፡፡
ሙሉ መረጃውን እንደደረሰን እናቀርባለን፡፡

source: eotcmk.or

The post ሰበር ዜና:- በአሰቦት ገዳም ደን ላይ የእሳት ቃጠሎ ተቀሰቀሰ appeared first on ሳተናው (Satenaw) -Latest Ethiopian News & Breaking News.