የአዉሮጳ ኅብረት የሁለት ቀን ጉባኤ

የአዉሮጳ ኅብረት የሀገር ዉስጥ ጉዳይ ሚኒስትሮች የሁለት ቀን ጉባኤ የኅብረቱ ዋና መቀመጫ በሆነችዉ ብራስልስ ጀምረዋል። ሚኒስትሮቹ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስጋትነቱ እየተጠናከረ በመጣዉ በሽብር እንቅስቃሴና በሕገወጥ ወደአዉሮጳ ስለሚገቡ ስደተኞች ጉዳይ እንደሚነጋገገሩ ይጠበቃል።