የቻይና ኤኮኖሚ

የቻይና ኤኮኖሚ ባለፉት ሁለት አሠርተ ዓመታት ባለሁለት አሀዝ እድገት በማስመዝገብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሁለተኛዋ ናት። ይኸው 12,2% የነበረው የእድገት መጠን ግን በሚቀጥሉት ጊዚያት በጉልህ ሊቀንስ እንደሚችል የምጣኔ ሀብት ጠበብት ገምተዋል። ይህም በቻይና ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ በዓለም ኤኮኖሚ ላይ ተፅዕኖ ሊያሳርፍ እንደሚችል ጠበብት ጠቁመዋል።