የመልካም አስተዳደር ሽልማት ለናሚቢያ ፕሬዚደንት

የሞ ኢብራሂም ድርጅት የመልካም አስተዳደር ሽልማቱን ትናንት እንደገና ለአንድ አፍሪቃዊ መሪ ሰጠ። የድርጅቱ ሽልማት ሰጪ ኮሚቴ እንዳስታወቀው፣ ዘንድሮ ለዚሁ ሽልማት የበቁት ተሰናባቹ የናሚቢያ ፕሬዚደንት ሂፊኬፑንዬ ፖሀምባ ናቸው።