የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ

የኢትዮጵያ መንግሥትን የሚቃወሙ 6 የኦሮሞ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በድሎናል ሲሉ አማረሩ ። የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለና በተለይ በአባላት ላይ ይደርሳል ስለተባለው እንግልት ቦርዱ እንዳልሰማ ተናግረዋል ።